ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትና

Recent Posts

የሐዋርያት መልስም "በእርሱ እንድንድን የሚገባን ሌላ ስም ከሰማይ በታች ለስው ልጅ አልተሰጠም።፣፣፣ የሚል ነበረ የሐዋ ስራ4:12።ይህን እውነት ሰምተው ወደ ተሻለ ኪዳን፣እንደ መመለስ ፣ጭራሽ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዳያስተምሩ እንዳይመሰክሩ አጥበቀው አዘዝዋቸው።ሓዋርያ ጴጥሮስ እና ዮሐንስ ግን ፣
★"ያየነው የሰማነው እውነት ልንተወው አንችልም★ "በማለት መለሱ።!
እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወትነው።ህይወትነቱ በዚህ ምድር የሚኖረንን ህይወት በመባረክ ብቻ የሚቀርየሚያልፍ አይደለም። እርሱ ህይወት ስለሆነ በእርሱ የሚያምኑ ቢሞቱእንኳን ህያዋን ናቸው። እርሱ ዘለዓለማዊ ሕይወት ነውና። በእርሱ የሚያምኑ አያፍሩም እንዲል መጽሐፍ በኢየሱስ ክርስቶስ ፍጽም እምነት ያላቸው ሁሉ ቢሞቱ እንኳን ህያዋናን ናቸው እርሱ ትንሳኤና ህይወት ነውና። ራሱ ኢየሱስ ከርስቶስ ሲናገር ዮሐ 11፡25 ኢየሱስም። ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤ እንዳለ።የሚያምኑበት ይነሳሉ የዘለዓለም ህይወትንም ይወርሳሉ። መነሳትስ ሁሉም ይነሳል ነገር ግን በክርስቶስ የሚያምኑ ለህይወት ለሚሆነው ደስታና ሰላም ላለበት ትንሳኤ ይነሳሉ። ከእርኛቸው ከክርስቶስ ጋርም ይከበራሉ። ነጩንም ልብስ ከለበሱ ህይወታቸውንም ለበጉ አሳልፈው ከስጡ ጋር በአንድነት ይከብራሉ።
«★በዋእየ ፍቅርከ ከመ ሥርወ አእዋም የብሰ ውሳጤ ሕሊናየ ነደ ወልብየ ጤሰ★» በፍቅርህ ሙቀት የልቤ ኃጢአት ደረቀ ሕሊናየ ተቃጠለ ልቤም ጤሰ እያሉ አመስግነውታል ★መልከዓ ኢየሱስ★።
ለአባቶቻችንን ያቃጠለው የክርስቶስ ኢየሱስ ፍቅር እኛንም ነክቶናል።ገናና ስሙም ለአለም እናውጃለን፣እንመሰክረሰለን።ዳሩ ግን ከአመንበት እውነት ወጥተን የዚህ አለም ፍልስፍና ላይ ትኩረት እንድንሰጥ የሚመክሩን ከአለም የሆኑ ስዎች፣ከመድኃኒታችን፣ከሕይወታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ እንድንለይ የሚዳክሩ ፣ስሙ እንዳንጠራ በስሙ እንዳናስተምር የሚያስጠነቅቁን የዘመናችን አይሁዳዊያን መልሳችን ከቅዱሳን አባቶች የተለየ አይደለም።ዳሩ ግን
★ሠናይ እገሪሆሙ ለእለ ይዜንው ሠናየ ዜና፡፡ መልካሙን የምሥራች የሚናገሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው፡፡ ሮሜ 10:15★። ተብሎ ተፅፏልና
ክርስቶስ በአባቱ ቀኝ ተቀምጦ አለምን በፍቅርና በፍትህ እየገዛ እያስተዳደረ እንዳለ ፃድቃንን በቀኙ፣ኃጥአን በግራው ለማድረግ ለፍርድ እንደሚመጣ ከኢየሩሳሌም እስከ ይሁደ፣ከሰማርያ እስከ አለም የመጨረሻ ደንበር የክርስቶስ ምስክር ነን።ከዚህ እውነት የሚለየን ሓይልም የለም።ሮሜ 8:38–39 ልክ እንድ አባቶቻችን ለእውነት ልንሞት ይገባል።የተሰጠን አላማ የእግዚአብሔር መንግስት ለማስፋፋት ነውና። ፡“የተጠራነው በስሙ ልናምን ብቻ ሳይሆን መከራንም ልቀበል ጭምር ነው”፡፡ፊሊ1፤29 ደቀ መዛሙርቱ « እኛስ ያየነውንና የሰማነውን ከመናገር ዝም ማለት አንችልም» / የሐዋ. ሥራ. 4፣2ዐ/ ስማችን እንዳይጠፋ፣እንዳይሰድቡን፣ በማለት ከአመንበት፣ ቤተ ክርስቲያን ከቆመችለት እውነት ወደ ኃላ ማለት አያስፈልግም።”
★አመ ትመጽእ ለኮንኖ ምስለ ደመ ገቦ አእጋር አማኅፀንኩ ነፍስየ ውስተ እዴከ ክቡር”★/መጽሐፈ ሰዓታት ገጽ ፪፻፵፩/
በዳግመኛ ምጽአትህ ጎንህ በጦር እንደተወጋ እጆችህና እግሮችህም እንደተቸነከሩ ሆነህ ለፍርድ ስትመጣ ነፍሴ በከበረ የእጅህ መዳፍ እረፍት እንድታገኝ አደራ እልሃለሁ/እማፀንሃለሁ/ማቴ 25:31/።ስለ ግርፋትህ፣ሞትህ፣መራብ፣መጠማትህ ሁሉ ብለህ ይቅር እንድትለኝ እለምንሃለሁ እንዲል።
ለአዳነን ላፈቀረን፣ከኃጢአታችን በደሙ ላነፃን ለመንግስቱ ወንጌል ካህናት እንድንሆን ላደረገ ኢየሱስ ክርስቶስ ክብርና ስልጣን ለዘለአለም ይሁን አሜን።
“እመሂ ስሕትኩ አንትሙ እለ በመንፈስ አርትዕዎ”
“የተሳሳትኩትም ቢኖር እናንተ በመንፈስ ያላችሁ አቃኑት”
★በሥጋ ያዩት ሰቅለውታል በመንፈስ ያዩት ሰግደውለታል።★
※ቅዱስ አግናጥዮስ ዘአንፆኪያ ምጥው ለአንበሳ በሮማዊያን ተይዞ እዲገደል ይዘውት እየሄዱ ሳለ ሁል ግዜ የኢየሱስ ክርስቶስ ስም ከአንደበቱ አይለይም ነበር።የሮም ወታደሮችም"ይህ ስም አታሳርፈውም?አይበቃህም?ብለው ጠየቁት።ቅዱስ አግናጥዮም "እንዴት አድርጌ የኢየሱስ ስም ከአንደበቴ ልለይው እችላለሁ በልቤ እኮ ነው የታተመው:የነገሰው አላቸው።በሮም እንደደረሰም በአናብስት ጉድጓድ አስገቡት።አናብስቱም ስጋ እና አጥንቱ ሳይቀር በሉት ነገር በመለኮታዊ ተአምር ልቡ ለብቻው ተረፈች። "የኢየሱስ ስም በልቤ ነው ያለው:የሰፈረው ብሎ የነገራቸው ወታደሮች ልቡ ለብቻዋ ሲመለከቱ"ኑ እንሂድና ኢየሱስ የሚል ስም በልቡ ላይ እንዳለች እንይ?ተባብለው ልቡን በቢላ ለሁለት ሲከፍሉት ""★ኢየሱስ★""የሚል ስም በወርቅ የተሰራ በልቡ ተገኘ ።ስለዚህም ነው ቅዱስ አግናጥዮስ/theophorus/ ተብሎ የሚጠራው።ክብር ለስመ አጠራሩ ይሁን ለዘለዓለም።
ጠላት አብዝቶ የሚጠላው ወዳጅም አብዝቶ የሚወደው ቢኖር ኢየሱስን ነው።
ኢየሱስ ማለት መድኃኒት፣ፈውስ ማለት ነው።ይህን ምስጢር ያልገባቸው አይሁድና አይሁዳዊያን ግን ለዚህ ስም በመቃወም ክርስቶስ እንዲሰቀል፣እንዲገደል ነገር ግን ለብዙ ዘመናት ሀብት እና ንብረታቸው እየዘረፈ ማስገባት ማስወጣት የከለከላቸውን ሽፍታ የነበረው በርባን እንዲፈታ ለምነዋል።ዳሩ ግን ያሳዝናል።
ዘመናትን ለሁለት የከፈለ፣ለዓለም ሕዝብ ሁሉ ከሞት ወደ ሕይወት፣ከጨለማ ወደ ብርሀን፣ከሲኦል ወደ ገነት ያሸጋገረ፣ለታመሙት ፈውስ፣ ለደከሙ ጉልበታቸው፣ለሞቱት ሕይወት የሚሰጥ ★ኢየሱስ★የሚል ስም ነው።ለዚህ ስም የማይገዛ በዚህ ስም ያልተሸፈነ ፉጡር ሊኖር አይገባም፣አለም የሚጠቀለለው በስሙ ስልጣን በፍቅሩ ብርታት ነውና ኤፌ1:9_10።ምክንያቱም ኢየሱስ ከስም በላይ ስም ስለ ሆነ።ስለዚህም ኢየሱስ ለሚልው ክቡር ስም በሰማይና በምድር ያሉት ፍጥረት ለዘለአለም ሊንበረከክ እና ሊገዛለት እንዲሁም ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቅ አባት፣ፈጣሪያችን እያለን እነረዘምራለን።ስሙ ነውና ሰው ያረገን ። የስሙም ጣዕም ዘወትር ከአንደበታችን የማይጠፋ ነው፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
★“ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ስም ለዘይጼውዖ፣ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ቃል ለዘያጸምዖ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ሥጋ ለዘይበልዖ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ደም ለዘይሰትዮ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ፄና ለዘያፄንዎ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ዝክር ለዘይነግር ዜናሁ ” “ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚጠራው ስሙ የጣፈጠ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚያዳምጠው ቃሉ የጣፈጠ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚበላው ሥጋው የጣፈጠ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚጠጣው ደሙ የጣፈጠ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ዜናውን ለሚነግር መታሰቢያው የጣፈጠ ነው ”
★ ያለው መቼ በከንቱ ሆነና (መጽሐፈ ምሥጢር፣ የዕርገት ምንባብ):: ስለሆነም ቤተክርስቲያን ስመ ክርስቶስን ከመጥራት የምትከለከልበት ጊዜ የለም አይኖርምም::
ኢየሱስ የሚል ስም ከአድማስ እስከ አድማስ፣ከአፅናፍ እሰከ አፅናፍ ዓለም ሲዘረጋ፣በዚህ ስም ሕሙማን ሲፈወሱ፣ሙውታን ሲነሱ፣ለምፃሞች ሲነፁ፣ዕውራን ሲያዩ፣መናገር የማይችሉትን አንደበታቸው ሲፈታ፣መሄድ የማይችሉትን እንደ እንቦሳ ሲዘሉ ፣በዚህ መልካም ስራ የቀኑት አይሁድና አይሁዳውያን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንዴት እንደ ሚገድሉት ፣ለዚህ ከስም በላይ ስም የሆነ ደግሞ እንዴት ከሰው ህሊና እንደ ሚረሳ ማሰብ እና ማብሰልሰል የዘወትር አላማቸው ሆነ።ስለዚህም ከእነ ስሙና ታሪኩ ለማጥፋት የተጠቀሙት ዘዴ እንደ ወንጀለኛ በመስቀል ተሰቅሎ እንዲሞት፣ስሙ ለሚጠሩትም ጌታ ኢየሱስን እንደ መድሓኒታቸው እንደ ንጉሳቸው ፣እንደ አምላካቸው የተቀበሉት እንዲሁም ቅዱስ ስሙን ሲመሰክሩ የተገኙት ደግሞ ሊዘረፉ፣ቤታቸው እንዲቃጠል፣ ሊገርፉ፣ሊሰየፉ፣ወንጌል ሳይሆን ወንጀል በሚሰብኩባት ምኩራብ ደግሞ ለማሳደድ ወሰኑ።ቢሆንም ግን ማንም በማይቀርበው ብርሃናዊ ዙፈን ተቀምጦ ጥልቁን ውቅያኖስ የሚመረምር፣አለምን በፍቅርና በፍትሕ የሚያስተዳድር ዘለአለማዊ ንጉስ እንዲገደል ማሰብ፣ይህን የማይጠፋ ስም ለማጥፋት መጣር ሞኝነት እንጂ ጥበብ አይደለም። ቅዱስ ጳውሎስ “
★ኦ አብዳን ሰብአ ገላትያመኑ አሕመመክሙ ከመ ኢትእመኑ በጽድቅ ከመ ያስተርኢ ለዓይን ኢየሱስ ክርስቶስ” “እናንተ ሰነፎች የገላትያ ሰዎች ሆይ ለጽድቅ እንዳትታዘዙ ማን አታለላችሁ? ቀድሞስ ኢየሱስ ክርስቶስ በዓይናችሁ ፊት እንደተሰቀለ ሆኖ ተስሎ ነበር” ያለው ከቶ ለማን ሆነና? ነገረ ክርስቶስ በዓይናቸው ፊት ተስሎላቸው ሳለ ላላስተዋሉት አይደለምን★?
ክርስትና ህይወት ናት፡ ክርስቶስ የህይወት ባለቤት ስለሆነ በእርሱም ስለተመሰረተች ህይወት ናት። በእውነት በህይወት ሊኖሩ የሚፈልጉ ሁሉ ህይወትና መንገድ እውነትም የሆነውን ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ በህይወትም ይኖሩ ዘንድ ክርስትና ታስፈልጋቸዋለች።
ከአንዳ አንዶች ልባቸው በትዕቢት የተወጠረ/እንደ ፈርኦን/ በስተቀር ፣ኩፉ ምኞታቸውን የዋጣቸው ልጓም እንደሌለው ፈረስ ወደ ፊት የሚነዱ፣እምነታቸው በስሜት እንጂ በመረዳት ያልተመረኮዘ፣ትውፊትና መፅሓፍ ቅዱስ ለይተው ያለወቁ ፣የአይሁዳዊያን ባህሪ ያላቸው ሰዎች ካልሆኑ በስተቀር ፣ክርስቶስ ኢየሱስን የማይናፍቅ ለስሙ የማይቀኝ፣ስለ ታላቅ ውለታው ከአእምሮ በላይ ስለሆነ ፍቅሩ የማይመሰክር፣ንጉሴ፣ አምላኬ፣መድኀኒቴ አንተ ነህ እያለ ለስሙ የማይገዛ ፍጥረት በዘመን ሊኖር አይገባም።ምክንያቱም ኢየሱስ ፈውስ መድሓኒት፣የእረፍት ብርሃን፣ሰላም፣ህይወት ስለ ሆነ ።ስለዚህ እርሱጌታ የማይናፍቅ ፣ማራናታ አሜን ጌታ ኢየሱስ ና እያለ የማይዘምር ሊኖር አይገባም። ማር 1፥37 ።1ቆሮ1:23
★ዕፍረት ምዑዝ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ኢየሱስ ክርስቶስ መአዛዉ ያማረ ሽቶ ነዉ”★።ኤፌ 5:2
አንድም ኢየሱስ ክርስቶስ ምዑዘ ባህሪይ ነዉ።”ንዑ ንስግድ ሎቱ፤እንሰግድለት ዘንድ”/ፊል 2:10/ “ወንዕቀብ ትዕዛዛቲሁ፤ትዕዛዙን እንጠብቅ ዘንድ ኑ”።”ከመ ይሥረይ ለነ ኃጣዉኢነ፤ኃጢአታችንን ያስተሰረይልን ዘንድ” ኑ /መጽሐፈ ቅዳሴ ንባቡና ትርጓሜዉ ገጽ ፹፪ ሉቃ 5:24።
የገሃንም ደጆች ያፈረስንበት የእሳት ባህር የተሻገርንበት ፣በሞቱ ሞትን ያሸነፍንበት ፣በትንሳኤው ትንሳኤችን ያረጋገጥንበት ፣ነብያት የሚናፍቁት፣መላእክት ያበሰሩት፣ሓወርያት የሰበኩት የእምነታችን ጅማሪና ፍፃሜ ንጉሳችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ እንዳንጠራ እንዳናመሰግን ለስሙ እንዳንገዛ ፣ስለ ዋለልን ውለታ ለአለም እንዳንመሰክር፣በስሙ ሕሙማን እንዳይፈወሱ እንደ ስምኦን ሉቃ 7:36:50 በበራችን ደጅ ቁመው እንዳንገባ እንዳንወጣ የሚከለከሉን ሰዎች :ተስፋ ቆርጠን ወደ ኃላ እንድንመለስ ደካማ ጎናችን የሚፈልጉ ተረፈ ፈሪሳዊያን ብዙ ናቸው።እንዚህ ከአባታቸው ከዲያብሎስ እንጂ ከእግዚአብሔር እንዳልሆኑ ከፍሬያቸው ይታወቃሉ።ታስታውሱ እንደሆነ ከልጅነቱ ጀምሮ ሸባ የነበረ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሲፈውስት በወቅቱ የነበሩ ሊቀ ካህናትና ፀሓፍት ፈሪሳዊያን "በማን ሓይል ወይም በማን ስም ነው ይህን ያደረጋቹሁት"በለው ጠይቀዋል
ጌታዬ መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! አንተን በበደልኩ ጊዜ ዕርቃኔን ወጣኁ፡፡ ጸጋዬ ተገፈፈ፡፡ አፈረኩ፡፡ በበለስ ቅጠልም ዕርቃኔን ሸፈንኩ፡፡ አንተ ግን አንተ ነኅና በማይለካ መውደድን ወደድከኝ፡፡ አዳም ሆይ ወዴት ነኅ ብለኽ ጠራኸኝ፡፡ እኔን ፍለጋም ወደኔ መጣኅ፡፡ ያንተን ትሰጠኝ ዘንድ የኔን ባሕርይ ገንዘብ አድርገኅ ፈለግከኝ፡፡ ዕርቃኔን የሸፈንኩባት ቅጠልንም ለዘላለም የሞት ፍሬ አይገኝብሽ ብለኅ ረገምክልኝ፤ ፈጽመኅም አጠፋኽልኝ /ማቴ.21:19/፡፡ የወይን ተክል ኾነኽም በጥላኅ አሳረፍከኝ /ዮሐ.15:1/፡፡ አባት ሆይ! አኹንም ከጥላኅ በታች ማደርን በየጊዜውም ጣፋጭ ፍሬውን ይኸውም ቅዱስ ሥጋኽን ክቡር ደምኽን እመገብ ዘንድ አድለኝ፡፡
“መኑ ይመስለከ፡ እምነ አማልክት እግዚኦ፡ አንተ ውእቱ ዘትገብር መንክረ፡ አርአይኮሙ ለሕዝብከ ኀይለከ፡ ወአድኀንኮሙ ለሕዝብከ በመዝራዕትከ ሖርከ ውስተ ሲኦል፡ ወአዕረገ ጼዋ፡ እምህየ ወጸጎከነ ምዕረ ዳግመ ግዕዛነ እስመ መጻእከ ወአድኀከነ፡፡
በእንተ ዝንቱ ንሴብሐከ፡ ወንጸርሕ ኀቤከ እንዘ ንብል፡ ቡሩክ አንተ እግዚኦ፡ ኢየሱስ ክርስቶስ እስመ መጻእከ ወአድኀንከነ፡፡” (ሥርዓተ ቅዳሴ)
አቤቱ ፈጣሪያችን፡ መድኀኒታችን እግዚአብሔር ሆይ፤ “አማልክት” ከተባሉ፡ አማልክት ከሆኑባቸው ከእነ ዜውስ፡ ከእነ አርጤምስ አንተን የሚያህል፡ አንተን የሚተካከል ማነው? አማልክት ከሆኑብን ከስስት፤ ከዝሙት፤ ከሐሰት አንተን የሚመስል፤ አንተን የሚተካከል ማነው?
እኒህ ሁሉ አማልክት ሕዝብህን ከክፉ ማዳን አይችሉምና፤ ሕዝብህን ከክፉ በማዳንም ድንቅን አላደረጉምና፡፡ አንተ ግን በከበረች ኀይልህ፡ እኛን ልታከብር፡ እኛ ከገባንበት ደይን (ሲኦል) ለማውጣት፡ ወደ ሲኦል ሄድኽ፡፡ እኛን ለመፈለግ በፍቅርህ ብዛት ወደ ምድር መጣህ፡፡ ፍቅርህ እውነተኛ ናትና “ወደ ምድር መጣሁላቸው፤ እሱ ይብቃቸው” ብለህ ፍቅርህን ሳትቆጥር፤ በደላችን ከምድር በታች (ሲኦል) ወስዳናለችና፡ እዚያም ሄድኽ፡፡ ክቡር እና ልዑል ለሆነ አባትህ ምርኮን ማረክህ፤ እኛን ወደ እርሱ አቀረብከን፡፡ እኛን ከከፋችው ቦታ አወጣኸን፡፡ ለዘለዓለም የሚሆን ነጻነትን (ጸጋን) ዳግመኛ ሰጠኸን፡፡ ጥንት የሰጠኸንን ነጻነት አንተን ላለመውደድ፤ ሕግህንም ላለማድረግ በጥመት ተጠቅመንበት ነበርና፡፡ አሁን ግን ወደን፡ ፈቅደን ለአንተ እንድንገዛ ከሰይጣን ባርነት፤ ያንተን ወደምትመስል ነጻነት መለስከን፡፡ ታዲያ እኛ ምን ብለን፡ ምን አድርገን እንመልስልህ? “የቡሩክ አብ ልጁ፡ ቡሩክ ወልድ” ብለን እናመስግንህ እንጂ፡፡ “እኛን ክፉ ከተባለው ሁሉ ጠብቀን” ብለን እንለምንህ እንጂ፡፡ “እኛን ከራሳችንም ጠብቀን፤ አድነን” ብለን እንለምንህ እንጂ፡፡ አንተ መጥተህ (ሰው ሆነህ) አድነኸናልና፡፡ አሁንም በመምህራን ትምህርት፤ በካህናት መሥዋዕት፤ በምዕመናን ጸሎት መጥተህ ታድነናኽና፡፡ አቤቱ ከአማልክት አንተን የሚመስል ማነው? አቤቱ ማረን!
ፍቅር!
በፍቅር ውስጥ ሰላም አለ በፍቅር ውስጥ ደስታ አለ በፍቅር ውስጥ እምነት አለ በፍቅር ውስጥ ተስፉ አለ በፍቅር ውስጥ እውነት አለ በፍቅር ውስጥ ትዕግስት አለ በፍቅር ውስጥ ጸጋ አለ በፍቅር ውስጥ እረፍት አለ በፍቅር ውስጥ ጤና አለ በፍቅር ውስጥ መዋሐድ አለ በፍቅር ውስጥ አንድነት አለ። ፍቅር ዘር ብሔር ቋንቋን አይለይም ፍቅር ቀይ ጥቁር ቆንጆ መጥፎ አይልም በፍቅር ውስጥ እንዲሁ መዋደድ እንዲሁ መፋቀር አለ። ፍቅር ሃብት ድኽነት ጥጋብ ረሃብ አይልም። ፍቅር ስሜትን ልቡናን ማንነትን የሚቆጣጠር በቃላት ሊገለጽ የማይችል ረቂቅ ነገር ነው ፍቅር ቀልድ አይደለም ፍቅር ደካማም ጠንካራም የማድረግ ኃይል አለው ፍቅር ከቃላት በላይ ነው ፍቅር ከስጦታ በላይ ነው ፍቅር ሁሌም እውነት ነው ፍቅር የሚከሰት እንጂ ሠው ፈልጎ የሚያመጣው አይደለም ፍቅር በልብ ውስጥ የሚያድግ ስሜት ነው ፍቅር አለምን የሚያሳይ ክስተት ነው ፍቅርን ሳያውቅ ያለፈ ሠው በሕይወት አልኖረም። ፍቅር የጦር መሳሪያ የለውም ግን ሁሉንም ያሸንፋል ፍቅር ባለበት ጭንቀት ተስፋ መቁረጥ ሰላም ማጣት አይታሰብም ዶፍ ዝናብ ቢዘንብ ሐሩር ጸሐይ ቢወጣ መብረቅ ቢወድቅ ፍቅር ካለ ስሜቱ ምንም ነው ምክንያቱም ፍቅር ከሚዳሰሰው ከሚጨበጠው ከሚታየው በላይ ነውና መከራ ቢያጋጥም ጨለማ ነግሶ ብርሃን የጠፋ ቢመስልም ፍቅር ካለ በማይታይ ድቅድቅ ውስጥ ጽልመት የማያሸንፈው አብርሆት ነግሶ ይታያል። ፍቅር ከምንናገረው ከምናወራው መግባቢያ ከሆነው ቃላችን በላይ ነው ፍቅር በሶስት ቃላቶች አጥሮ ነገር ግን ውስጡ ረቂቅ ምስጢራትን የያዘ ድንቅ ምጡቅ ቃል ነው። ፍቅር እንደሁኔታው የሚገለጥ በሰው ልጆች ሁሉ አካል ውስጥ ያለ የተሰወረ አንድ ቀን የሚገለጥ ንዝረት ነው ፍቅር ከምንጽፍለት ከምንናገርለት ከህሊናችን በላይ የሆነ ድንቅ ነው ሰማይ ወረቀት ሆኖ ምድርም ቀለም ሆና ስለፍቅር ጽፈን እንጨርስ ዘንድ አንችልም ምክንያቱም ሰማይና ምድር የማይወስኑት ሰማይና ምድርን የሚወስን ከላይ ጽርሐ አርያም ከስር ጥልቅ በርባሮስን የመላ የርሕቀት ጥግ ወሰኑ የማይታወቅ ጌታ እግዚአብሔር ፍቅር ነውና ፍቅር ባለበት ተስፋ እምነት ሰላም ነጻነት ሁሉም በሁሉም የሆነ ጌታ እግዚአብሔር አብ አለ ፍቅር ባለበት ነጻነት ቤዛ አዳኝ በደሙ የዋጀን በቤዛነቱ የታረቀን በኩረ ትንሳኤ የተባለ ሊቀካህናት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አለ ፍቅር ባለበት አንድ የሚያደርገን በውሃ ጥምቀት በቅብዐ ሜሮን የተቀበልነው የሚያዋሕደን አንድ የሚያደርገን የሚያከብረን ከኃጢአት አርቆ የቤተክርስቲያን አካል ያደረገን ያነጻን የቀደሰን ያከበረን መንፈስ ቅዱስ አለ። ኡፍፍፍፍ በፍቅር ህብረት ውስጥ መኖር ምንኛ መታደል ነው!በአንድነት በሶስትነት የሚመለክ ቅድስት ሥላሴ በእውነተኛው ፍቅር ያጽናን ሰላሙን ያብዛልን አሜን!!
DN ሸዋፈራው
ይቆየን
ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ከወንድሞች ሁሉ የማንስ እኔ ባሪያህ ስለሠርግኽ ሳስብ እጅግ እፈራለኹ ስለ ግርፋትህ ፣ሞትህ ፣ መራብ ፣መጠማትኽ ሁሉ ብለህ ይቅር እንድትለኝ እየለመንኩኽ በደብረ ጽዮን እንድምተኛ ታረገኝ ዘንድ እሻለው!!
“ እባክህ፥ መባረክን ባርከኝ፥ አገሬንም አስፋው፤ እጅህም ከእኔ ጋር ትሁን፤ እንዳያሳዝነኝም ከክፋት ጠብቀኝ ብሎ የእስራኤልን አምላክ ጠራ፤ እግዚአብሔርም የለመነውን ሰጠው።”
— 1 ዜና 4፥10
ፍቅር ቁስል ነው!

እውነቱ ይኽ ነው ፣ ፍቅር የሚለካው በልባችን ላይ በተወው ቊስል ልክ ነው።
እጅግ የምንወዳቸው ሰዎች አሳምመውን ይሆናል።
እኛም እጅግ የሚወዱንን ሰዎች አሳምመን ይሆናል።
ምክንያቱም ፍቅር የሚታየው በታገስ ነው ቊስል ውስጥ ነው።

ፍቅር የሚታወቀው የተለዋወጥናቸውን ቃላት ሳይሆን በምንታገሠው ቊስል ፣ በተሰማን የውስጥ ሕመም ፣ በከፈልነውን መሥዋዕትነትና በተካፈልነውን ብርሃን ነው።

ከትንሣኤው በኋላ በሐዋርያቱ ፊት የተገለጠው ክርስቶስ ኢየሱስ እርሱ የሚወዱት ጌታ እንደሆነ ለማስረዳት ያሳያቸው የትንሣኤው ድል ማብሠሪያ መለከት አይደለም ፣ የፍቅሩ ማስረጃ ቊስሉ ነበር።
"ወደ እኔ ኑ ቊስሌን ዳስሱ ፣ እጃችሁንም ስለ እናንተ ፍቀር በቆሰልሁት ቊስል አስገቡ" ነበር ያላቸው።
አታስታውሱኝም? አላወቃችሁኝም? እስከ ሞት ድረስ የወደድኳችሁ እኔ ነኝ። ለፍቅሬ ማስረጃ እንዲሆናችኹ ደግሞ ቊስሌን ተመልከቱ! ነው ያላቸው።
ፍቅር ቊስል ነው።
በእግዚአብሔር መንግሥት ክብርና ምስጋና የምናገኘውም በምድር ሳለን በነበሩ ስኬቶቻችንና ባስገኘናቸው ውጤቶቻችን ሳይሆን በታገሥናቸው መከራዎችና በተሰቃየንባቸው ሕመሞች ልክ ነው።

ለዚህም ነው በአበው መጽሐፍ አንድ ቅዱስ አባት ለረጅም ዓመት በሰውነትዋ ላይ ቆስሎ የምትሰቃይን ሴት ሊጠይቁ ሲሔዱ
"እዩት ቊስሌን አጎንብሰው ቢያዩት አጥንቴ ይታይዎታል" አለቻቸው።
እርሳቸውም ጎንበስ ብለው "ብዙ ዓመት በታገስሽው በቊስልሽ ውስጥ የሚታየኝ አጥንት ሳይሆን ገነት ነው" አሏት።
ጌታ በፍቅር ውስጥ ያለውን መከራ ለትዕግስት አድርጎልን መንግስቱን እንዲያወርሰን ቅዱስ ፈቃዱ ይሁን አሜን!
ይቆየን
"አንተ አምላኬ ነህ አመሰግንህማለሁ። አንተ አምላኬ ነህ፥ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ፤ ሰምተኸኛልና፥ መድኃኒትም ሆነኸኛልና አመሰግንሃለሁ።" (መዝ ፲፲፯(፲፲፰) ፥ ፳፰)
ችግሮች ሲገጥሙህ ምን ሊያስተምሩህ እንደመጡ ማወቅ አለብህ፤ ለምን ወደ ህይወትህ እንደመጡ ሳታውቅ ከቀረህ ግን ደጋግመው መምጣታቸው አይቀርም!
ከማንነትህ ጋር የምትተዋወቀው ችግር ሲገጥምህ ነው፤ አንዳንዴ ፈጣሪ በምን መንገድ ሊያስተምርህ ወይ ታላቅ ሊያደርግህ እንዳሰበ አታውቅም። ሁኔታዎች ላያስደስቱህ ይችላሉ ግን እመነኝ ወዳጄ እንደዚህ አይቀጥሉም!
ወአስተራይከ ጸጋከ ላዕለ ሐዋርያት እንዘ ጉቡአን እሙንቱ ውስተ አሐዱ ቤት ወረደ ላዕሌሆሙ መንፈስ ቅዱስ ከመ ዘእሳት ወተናገሩ በነገረ ኵሉ በሐውርት። ውእተ መንፈስከ ፈኑ ዓማዴ ሰማይ ወምድር ባርክ ማኅበረነ በኵሉ ጊዜ ወበኵሉ ሰዓት። በአሐዱ ወልድከ ዘቦቱ ለከ ምስሌሁ ወምስለ ቅዱስ መንፈስ ስብሐት ወእኂዝ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለመ ዓለም አሜን።

ሊጦን_ዘእሑድ እንኳን ለበዐለ መንፈስ ቅዱስ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።መንፈስ ቅዱስ ዘወትር በኛ ላይ ጸንቶ ይኑር አሜን!!!
“ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፤ እግዚአብሔር ፍቅር ነውና። በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፤ በእሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና፤ ፍቅር እንደዚህ ነው። እግዚአብሔር ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኀጢአታችን ማስተሥርያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደላከ እንጂ እኛ እንደወደድነው አይደለም። ወዳጆች ሆይ! እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ ርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል። እግዚብሔርን ማንም ከቶ አላየውም፤ ርስ በርሳችን ብንዋደድ እግዚአብሔር በእኛ ይኖራል፤ ፍቅሩም በእኛ ፍጹም ይሆናል። (1ኛዮሐ. 4-8-2)
"ትሕትና ያሉህን ትንንሽ ነገሮች ማሰብ ሳይሆን፣ የራስህን ታናሽነት አምኖ መቀበል ነው"
https://fb.watch/5MyUcLVCeu/
‹‹እያዩት ወደ ሰማይ አረገ››ሐዋ 1፡29 ስብከት በዲያቆን ሸዋፈራው
ነው መባሉ ። ማቴ 12:24 ሳምራዊ ነው ጋኔን አለበት መባሉ ። ዩሐንስ 8:48 ።
እነዚህ ሁሉ ነቀፌታዎች ስድቦች ወደሰማይ ባረገ ጊዜ በአባቱ ቀኝ
በተቀመጠ:ጊዜ ተደምድመዋል ።
በአባቱ ቀኝ መቀመጥ ማለት " እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ
ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥ነገር
ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥ፊል 2:6–7
"ተብሎ እንደተጻፈ ራሱን ባዶ ማድረጉ ተጠናቀቀ ማለት ነው ። በዚያ ሁኔታ
ውስጥ ሆኖ የሰብዓዊ ባህርይ ድካሞችን ታግሳል ፣ ተርባል ፣ ተጠምቷል ፣
ደክሟል እንዲሁም አንቀላፍቷል ። ነገር ግን በአባቱ ቀኝ ሲቀመጥ እነዚህ ሁሉ
ፍጻሜያቸው ሆነ ። የተያዘበት ፣ የተሰደበበት ፣ የተንገላታበት እና የተሰቀከበት
ድካም ሁሉ ተፈፀመ ።
በዳግም ምጽአት በኃይልና በክብር ይመጣል ።
ይቆየን
በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ ምን ማለት ነው?
በእርግጥ ያረገው በአካል ነው ። እግዚአብሔር መለኮት አይወርድም ወይም
ዐያርግም ። እግዚአብሔር 《መለኮት》 ከላይም ከታችም በመካከልም ፣
በሰማይና በምድር እንዲሁም በሁለቱም መካከል አለ ። ሁሉን የሞላ እና
በሁሉም ቦታ የሚኖር ነው ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ቅዳሴ ውስጥ ።
《በአካል ወደ ሰማይ ባረግህበት ዕርገትህ ላይ》 እንደምንለው በአካል ወደ
ሰማይ ዐርጓል ።
ደቀመዛሙርቱ በአካል ሲያርግ አይተውታል " ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ
እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው። ሐዋ 1:9 "
በእርግጥ ይህ ዕርገት በአካል ነበር ምክንያቱም መለኮትን መመልከት
አይችሉም ። ጌታችን በከበረ መንፈሳዊ አካል ዐረጓል ።ይህ አካልሐዋርያው
ለቆሮንቶስ ሰዎች በላከው መልዕክቱ እንደተናገረው: እኛ የምንነሳበት መንፈሳዊ
አካል ነው ።
" የዚያንም የመሬታዊውን መልክ እንደ ለበስን የሰማያዊውን መልክ ደግሞ
እንለብሳለን። 1ኛ ቆሮ 15:49 " ይህ እኛ የምንነሳበት መንፈሳዊ አካል ነው
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በትንሳኤው ይዞት የተነሳውን አካል የሚመስል ነው "
እርሱም ሁሉን እንኳ ለራሱ ሊያስገዛ እንደሚችልበት አሠራር፥ ክቡር ሥጋውን
እንዲመስል የተዋረደውን ሥጋችንን ይለውጣል።ፊል 3:21 "
በዕርገት ተአምር የመሬት ስበት ኃይል የሚፈታተነው አይደለም ። ይህ ተአምር
ለመሬት የስበት ሃይል ክስተት ተገዢ ያልሆነ በከበረ መንፈሳዊ አካል ላይ የሆነ
ተአምር ነው ። ለመሬት የስበት ሃይል ተገዢ የሆነ ቁሳዊ አካል ብቻ ነው:
ስለዚህም ጌታችን ወደሰማይ ያረፈበት ሰማያዊው አካል ከስበት ጋር ምንም
ግንኙነት የሌለው ሲሆን የመሬት የስበት ሃይል አልተፈታተነውም ነበር ። እኛም
በተመሳሳይ በትንሳኤ ሙታን ሕያዋን ሆነን የምንቀርበው ጌታ በአየር ለመቀበል
ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን ። 1ኛ ተሰ 4:17 ይህም የመሬት ስበት ኃይል
ፈተና አይሆንበትም ምክንያቱም እኛ በምንነሳበት በመንፈሳዊ አካል ላይ የስበት
ኃይል ምንም ኃይል የለውም ። ይልቁንም ከትንሳኤው:በኋላ የጌታችን የኢየሱስ
ክርስቶስ ዕርገት ምንኛ ይልቅ!
"ወደ ሰማይ ዐረገ "የሚለው ቃል ወደ ሰማየ ሰማያት ዐረገ ማለት ነው ። ከእርሱ
በቀር ወደ ሰማየ ሰማያት ማንም ፈጽሞ ዐላረገም ። ኤልያስ እና ሄኖክ እንኳን
ቢሆኑ ወደዚህ ዐላረጉም ። ጌታችን ለኒቆዲሞስ " ከሰማይም ከወረደ በቀር ወደ
ሰማይ የወጣ ማንም የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው።
ዮሐንስ 3:13 " 《ሰማየ ሰማያት》 የሚለው አገላለጽ ሰሎሞን ቤተ መቅደስ
በሚያንጽበት ወቅት በጸለየው ፀሎት ውስጥ እግዚአብሔርን " በውኑ
እግዚአብሔር ከሰው ጋር በምድር ላይ ይኖራልን? እነሆ፥ ሰማይ ከሰማያትም
በላይ ያለው ሰማይ ይይዝህ ዘንድ አይችልም፤ ይልቁንስ እኔ የሠራሁት ቤት
እንዴት ያንስ! 1ኛ ነገ 8:27 "ባለው ጊዜ ተገልጿል ። በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ
"ሃሌ ሉያ። እግዚአብሔርን ከሰማያት አመስግኑት፤ በአርያም አመስግኑት።
መላእክቱ ሁሉ፥ አመስግኑት፤ ሠራዊቱ ሁሉ፥ አመስግኑት።ፀሐይና ጨረቃ፥
አመስግኑት፤ ከዋክብትና: ብርሃን ሁሉ፥ አመስግኑት። ሰማየ ሰማያት፥ አመስግኑት
የሰማያት በላይም ውኃ።መዝ 148:1–4 "
☞☞ በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ
ይህ እውነት በአዲስ ኪዳን በርካታ ቦታዎች እንዲሁም በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ
ባሉት ትንቢቶች ላይም ተጠቃልሎ ተቀምጧል ።።
ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተናገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ
በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ። ማር 16:19
እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ ምሳሌ ሆኖ፥ ሁሉን በስልጣኑ ቃል
እየደገፈ፥ ኃጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ፤
ዕብ 1:3
ከተናገርነውም ዋና ነገሩ ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ
የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን፤ ዕብ 8:1
የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን
ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል
ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና። ዕብ 12:2
ኢየሱስም። አንተ አልህ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ከእንግዲህ ወዲህ የሰው
ልጅ በኃይል ቀኝ ሲቀመጥ በሰማይም ደመና ሲመጣ ታያላችሁ አለው። ማቴ
26:64 ይህ ቃል የተነገረው በሸንጎው ፊት በኢየሱስ ክርስቶስ ነው ።
እነሆ፥ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ
አለ። ሐዋ 7:56 ይህ ቃል ቅዱስ እስጢፋኖስ በሚወገርበት ጊዜ " መንፈስ
ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር
ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ ሲያይ ። የተናገረው ነው ።
እግዚአብሔር ጌታዬን። ጠላቶችህን ለእግርህ መቀመጫ እስካደርግልህ
ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው። መዝ 110:1
ነገር ግን በእግዚአብሔር ቀኝ መቀመጥ ማለት ምን ማለት ነው? እግዚአብሔር
ቀኝ ወይም ግራ የለውም ምክንያቱም ቀኝና ግራ ያለው የተወሰነ ነገር ነው
እግዚአብሔር ደግሞ አይወሰንም ። ከዚህ ባሻገር በእግዚአብሔር ቀኝ ሌላ
አካል እንዲቀመጥ የሚያስችል ሌላ አካል የለም ። እግዚአብሔር ወልድ በአባቱ
ቀኝ ቢቀመጥና ይህንም ቦታ ይዞ በመቀመጥ ትርጉም ከተረዳነው " እኔ በአብ
እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ እመኑኝ፤ ባይሆንስ ስለ ራሱ ስለ ሥራው እመኑኝ።
ዮሐንስ 14:11 " የሚለው የጌታችን ቃል ተግባራዊ አይሆንም ነበር ።
☞ ታዲያ 《ቀኝ》 የሚለው ቃል ምን ማለት ነው?
በመጽሐፍ ቅዱሳዊ የቃላት ስያሜ መሠረት ቀኝ ማለት ኃይልን ቅድስናን ወይም
ክብርን የሚያመለክት ነው ።ኃይልን ከመግለፅ አኳያ መዝሙረኛው ዳዊት "
የእግዚአብሔር ቀኝ ኃይልን አደረገች። የእግዚአብሔር ቀኝ ከፍ ከፍ አደረገችኝ፤
የእግዚአብሔር ቀኝ ኃይልን አደረገች። አልሞትም በሕይወት እኖራለሁ እንጂ፥
የእግዚአብሔርንም ሥራ እናገራለሁ። መዝ 118:15–17 " 《 በቀኝህ አድን
አድምጠኝም። መዝ 108:6፣ 60:5 》 ብሏል
።ዳግመኛም ቃሉ ያዕቆብ
የዮሴፍን ልጆች አንደባረከበት እና እጁን በታናሹ ራስ ጭኖ እንዳከበረው ለክብር
ይሆናል ። ይህ ማለትም ታላቅ ክብር ሰጠው ማለት ነው ። ዘፍ 48:17–19
ይህ መዝሙረኛው "ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች "መዝ 45:9 ባለጊዜ መናገር
የፈለገው ማለት ነው ። በምሳሌያዊ አነጋገር ይህ ቃል ለቅድስት ድንግል
ማርያም የተሰጠውን ክብር ያመለክታል ። በተመሳሳይ ትርጉም መዝሙረኛው "
እግዚአብሔር በቀኝህ ነገሥታትን በቍጣው ቀን ይቀጠቅጣቸዋል።
መዝ 110:5 " ብሏል ።
በፍርድ ቀንም እግዚአብሔር ጻድቃንን በቀኙ ኃጥአንን በግራው ያቆማቸዋል ይህ
ማለትም ጽድቅንና ክብርን ያመለክታል ማለት ነው ።ስለዚህም የገነት ቃል ኪዳን
በመስቀል ላይ ሆኖ የተቀበለውን ወንበዴ "በጌታ ቀኝ የተሰቀለው ወንበዴ "ብለን
እንጠራዋለን ። በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ የዮሐንስን መወለድ ለዘካርያስ
የነገረው የጌታ መልአክም እጅግ ያማረ ማስረጃ ነው ።
ስለዚህም "የእግዚአብሔር ቀኝ "ማለት የእግዚአብሔር ኃይል ፣ ጽድቅ ፣ ክብር ማለት ሲሆን
"መቀመጥ "ማለት ደግሞ የማይለወጥ የተወሰነ ማለት ነው ።
ጌታችን ወደሰማይ ሲያርግ ኃይሉ ግርማው እና ክብሩ ልክ እንደበፊቱ
ያልተለወጠ የተወሰነ ነው ። ይህ ማለት ከምቀኝነት የተነሳ በሐሰት የደረሰበት
ነቀፌታዎችና ስድቦች ሁሉ ለምሳሌ ፦ አሳች መባሉ ። ማቴ 27:62 ፣ ሰንበት
አያከብርም መባሉ ። ዮሐንስ 9:16 ፣ አጋንንትን የሚያወጣው በብዔል ዜቡል
፨፨፨ ትንሿ ቤተ-ክርስቲያን ፨፨፨
ክርስትና እና ሮማን-ቲሲዝም
(CHRSTIANITY VS ROMANTICISM)
(Abraham Bekele እንደ ጻፈው)
የዓለም ጾታዊ ፍቅር ታሪክ ቢተረክ በኹለት ዘመን ይከፈላል ቅድመ ሮማን-ቲሲዝም እና ድኅረ ሮማን-ቲሲዝም። መሠረታዊ የሆነውን የሰውን ልጅ የፍቅር እና የግንኙነት እሳቤ ከቀየሩ እና መልክ ካስያዙ ዘመናት ከ17-19 መቶ ክፍለ ዘመን ያለው ትልቁን ስፍራ ይይዛል። ጆርጅስ ፍሎሮቭስኪ "አንድን ሰው ሙሉ ሰው አድርጎ የሚሰራው በሚኖርነት ማሕበረሰብእ ውስጥ ያሉ ትውፊቶች ናቸው" ይላል። ይሄ ፍጹም እውነት ነው። አንድን ሰው በማኅበረሰብእ ውስጥ ያሉ ጥሩም ይሁን መጥፎ ትውፊቶች ይሰሩታል።
በ17 መቶ ክፍለ ዘመን የተነሳ La Rochefoucauld የተባለ ፍልሱፍ "አንድ ሰው ስለ ፍቅር ሰምቶ የማያውቅ ቢሆን ፍቅርን ላያውቅ ይችል ይሆናል" ይላል። ይህ ትንሽ ለመቀበል ቢጸንም እውነት አለው። በአንድ የአውሮጳ ማኅበረሰብእ ፍቅር አበባ በመስጠት ቢገለጥ አንድ ኢትዮጵያ ውስጥ ላለ ሰው 10 ከብት በመዝለል ሊገለጥ ይችላል። ስለዚህ በአንድ ማኅበረሰብእ ውስጥ ያለ አንድ ሰው ስለ ፍቅርም ይሁን ስለ ጋብቻ ያለውን እሳቤ እና ያንን እንዴት እንዲገልጥ ከወጣበት ማኅበረሰብእ ይማራል። ወደደም ጠላም።
አሁን በሀገራችን በዓለምም ያለው እሳቤ ደግሞ ለብዙ መቶ ዓመታት አብዝቶ በተሰራባቸው በሮማንቲሲዝም ዘውግ ልብወለዶች የተቃኙ ናቸው። እነዚያ ልብ ወለዶች በዘመኑ አብዝተው የተወደዱ ነበሩ። የመጀመሪያው ምክንያት ደግሞ እነዚህን ልብ ወለዶች ሲያዘጋጁ የነበሩት በዕውቀት ደረጃቸው ትንሽ ከነበረው ማኅበረሰብእ ሻል ያለ ስለ ነበር ነው። አንዳንዶቹ ሥራ ፈቶች የነበሩ ነገር ግን የንግግር እና የጽሑፍ ጥበብን (Rhetorics) የተማሩ ስለነበሩ በጽሑፎቻቸው እና በንግግራቸው ወደ ማሕበረሰቡ ልብ ሰጥመው ገብተዋል። ከጸሐፊዎቹ መካከል አንደኛው እና ትልቁ ጎተ(Goethe) ነው። ሌሎቹም ቢሆኑ ፈላስፎች እና ሳይንቲስቶች ነበሩ። የዚህ ዘውግ ጸሐፊዎች ታዲያ መጀመርያ የሚፈጥሩብን ነገር ምናባዊ(Ideal) የሆነ የግንኙነት ቅንጣቶችን (Elements) ነው፤ የነፍስ አጋር (Soul mate)፣ የፍቅር በሩካቤ ሥጋ መገለጥ፣ ፍቅርን በተፈጥሮ ካሉ መስተጋብሮች ማስተሳሰር፥ ለምሳሌ ባህር ዳርቻ ላይ፣ አመሻሽ ላይ ሰማዩ ሲጠቁር ያለ ድባብ ለፍቅር የተመቹ እደሆኑ መስበክ የመሳሰሉት ናቸው። በእነዚህ ነገሮች ከተጠመድን በኋላ መሬት ላይ ባለው እውነታ እና በሥነ ጽሑፍ ውስጥ ባለው ዓለም መካከል ያለውን ልዩነት መለየት እስካንችል ድረስ እንታወራለን። ስለዚህ በሥነ ጽሑፉ ውስጥ ያለውን ምናባዊ ዓለም በሕይወታችን እንዲኖር እንጠብቃለን። እውነታው ግን ሥነ ጽሑፉ ብዙውን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዎቻችንን ይውጣቸዋል። ለምሳሌ በሥነ ጽሑፉ ውስጥ ልብስ ስለማጠብ፣ ምግብ ስለማብሰል፣ ውሃ ስለመቅዳት፣ ልጅ ስለማሳደግ፣ ውሳኔዎች ላይ ስለመወያየት የመሳሰሉት ወሳኝ የሕይወት ኩነቶች አይጻፉም ግን እነዚህ በተግባራዊው ሕይወት ትልቅ ተጽእኖ ያላቸው ናቸው። ይህ የሥነ ጽሑፍ ፍልስፍና ቀጥሎ ደግሞ በፊልሞች እና በድራማ መጣ። ስለዚህ ይህ Ideal የሆነ አስተሳሰብ የዓለም የጾታ ግንኙነት ታሪክ ቀየረ። አሁን ላለው ነባራዊ ሁኔታ ይህ መልስን የሚሰጥ ነው። ሰዎች ለምን ይፋታሉ ? ምክንያቱም በፊልም እና በሥነ ጽሑፍ ውስጥ የሚስሉትን ትዳር እና የፍቅር ሕይወት በእውነት በተግባር መሬት ላይ ወርዶ ስለማያገኙት። እኛ አማርጠን ከምናገባው በarranged marriage የሚዳሩ የአባቶቻችን እና የእናቶቻችን የጋብቻ ሕይወት ዘላቂ እና ደስታ የመላበት ነበር። ስለዚህ በእኛ እና በአባቶቻችን መካከል መሠረታዊ የአስተሳሰብ ልዩነት እንዳለ ለመገንዘብ አይከብድም።
ክርስትና እና ነባራዊው እሳቤ
ክርስትና ማዕከል የምታደርገው ድኅነትን ነው። ስለዚህ የትኛውም የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ከሥጋዊ ፈቃድ እና ሕይወት ባለፈ ሰማያዊውን መንግስት የሚያስብ ነው። ክርስትና በዓለም የሚከተለው የአሉታዊ ፍልስፍና(Philosophy of pessimism) ነው። ጌታ "በዚህ ዓለም ስትኖሩ መከራ አለባችሁ" ካለው ይጀምራል። ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን ለሥጋ የሚመች ምናባዊ ዓለም(Ideal world) ፈጥራ ሥጋዊ ደስታን ስታከፋፍል አትከርምም። ይልቅ ክርስቶስን የምንመስልበትን ሕይወት ትሰጠናለች እኛም አማርጠን እንኖረዋለን። ስለዚህ ቤተ ክርስቲያናዊ ልብ ይዘን ከኖርን የትኛውም ሕይወት ደስታችንን የሚቀማን መስሎ አይታየንም። በውጣ ውረዶች ኹሉ "ወሶበ እደክም አሜሃ እጸንሕ፤ ስደክም ያን ጊዜ እበረታለሁ" እያልን ፈተናዎቹን እንሻገራቸዋለን።
በክርስትና ክርስቶስን መስለን ከምኖርበት ሕይወት አንደኛው የጋብቻ ሕይወት ነው። በጋብቻ የሚኖሩ ሰዎች ክርስቶስ በዕለተ ዐርብ መልዕልተ መስቀል ላይ ከቤተ ክርስቲያን ጋር ሲሞሸር አይተው እርሱን መስለው የሚኖሩበት ሕይወት ነው። ስለዚህ ክርስቲያኖች ሲኖሩ እንደ ዓለማውያን እና የዘለዓለም ሕይወትን ተስፋ እንደማያደርጉቱ አይደለም። ፍጹም ክርስቶስን መስለው ነው። ስለዚህ ቅዱስ ጳውሎስ "ወዘልፈ ንጸውር ሞቶ ለክርስቶስ በሥጋነ፥ ዘወትር የክርስቶስን ሞቱን እንሸከማለን" እንዳለ ዘወትር የክርስቶስ የማዳን ግብር በእኛ ይታይ ዘንድ ፈጽሞ ክርስቶስን እንመስለዋለን። ስለዚህ መነኰሳት በገዳም ባሕታውያን በዱር በበረሀ የሚቀበሏቸው መከራዎች ከክርስቶስ አንድ የሚያደርጋቸው እርሱን የሚያስመስሏቸው ናቸው። ሰማዕታትም ቢሆኑ ደማቸውን ማፍሰሳቸው እርሱን የሚያስመላቸው ነው በመልክአ ኢየሱስ "አኃዊከ ሰማዕታት ቈላተ ሕማማት ወረዱ" ብለን ክርስቶስን በመከራው ስለመስሉት ሰማዕታት ወንድሞችህ እንላቸዋለን። ስለዚህ በጋብቻ ሕይወት የሚኖሩ ክርስቲያኖችም መከራውን ይጠብቁታል፣ ይዋጉታል፣ ድል ይነሱታል ጸጋ መንፈስ ቅዱስን፣ ቁመተ የማንን የቀበሉበታል። ቤተ ክርስቲያንም ስታጋባ "ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ" ብላ ቃል ታስገባለች። ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን እንዴት ወደደ? እስከ ሞት ድረስ !! ስለዚህ መከራ የጋብቻ ሕይወት አንደኛው ክፍል መሆኑን ማመን ይገባናል፤ ይህች የገብሬ መጽሐፍ ለጋብቻ ሕይወት መሞትን የምትሰብክ ናት። ዘመኑ ሲፈልገው የነበረው ነገር ይኸው ነው፤ የምዕራባውያን ግርዶሽ የተመረገበት የዐይናችንን ሞራ ገፎ ሕይወትን እና ክብረ መንግሥቱን እንድናይ የምትጋብዝ ናት። በትዳር ላሉ ሰዎች፣ ለማግባት ላሰቡቱ ገዝታችኹ ብትሰጡ መንገዱን ጠቆማችኹ፣ ግርዶሽ ገፈፋችኹ ማለት ነው።
ገብሬ አንተንም የልፋትህን ዋጋ እግዚአብሔር ያስብልህ !!
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘእንዚናዙ ለንስሓ ልጁ በሰርጓ ቀን መገኘት ባለመቻሉ የላከላት ደብዳቤ

“ልጄ! ለሰርግሽ የነፍስ አባትሽ እኔ ጐርጐርዮስ ይህን ግጥም ስጦታ አድርጌ ልኬልሻለሁ፡፡ አባት ለሚወዳት ልጁ ሊሰጣት የሚችለው የተሻለው ምክርም ይህ እንደ ኾነ አምናለሁ፡፡

“ኦሎምፒያታ ሆይ፥ እውነተኛ ክርስቲያን ለመኾን ያለሽን ፍላጎት ዐውቃለሁና በደንብ አድምጪኝ! እውነተኛ ክርስቲያን እንዲሁ መኾንን የሚመኝ ብቻ ሳይኾን እንደዚያ ለመኾን ሊጥር ይገባዋል፡፡

“ከኹሉም በላይ፥ እግዚአብሔርን ልታከብሪውና ልትወጂው ይገባሻል፡፡ ከእርሱ ቀጥሎም በቅዱስ ወንጌል እንደ ታዘዘው እንደ ጌታችንና መድኃኒታችን [ኢየሱስ ክርስቶስ] አድርገሽ ባልሽን ልታከብሪውና ልትወጂው ይገባሻል፡፡ ስለዚህ እጠይቅሻለሁ! ጌታዋንና ፈጣሪዋን [ኢየሱስ ክርስቶስን] የማታከብርና የማትወድ ሴት በዚህ መንገድ ባልዋን እንዴት አድርጋ ልታከብረውና ልትወደው ትችላለች?

“በጋብቻሽ ውስጥ የትዳር አጋርሽ ይኾን ዘንድ እግዚአብሔር መርጦ ለሰጠሽ ባል ያለሽ መውደድ፣ ስሜትና ፍቅር እጅግ ኃያል ሊኾን ይገባዋል፡፡ ይህ ሰው አሁን የሕይወትሽ ዓይን፣ የልብሽም ደስታ ነውና፡፡

“እግዚአብሔርን እንደምትወጂው፥ ባልሽንም ያለ ቅድመ ኹኔታ ልታከብሪውና ልትወጂው ይገባሻል፡፡ አንቺ ሴት እንደ ኾንሽና ታላቅ የኾነ ዓላማና ግብ እንዳለሽ፥ ኾኖም ዓላማሽና ግብሽ የቤትሽ ራስ ሊኾን ከሚገባው ባልሽ የተለየ እንደ ኾነ ዕወቂ፤ ተረጂም፡፡ ባንቺ ዕድሜ ላይ ያሉት አንዳንዶች ኹለቱም ፆታዎች እኩል [ራስ ናቸው] ብለው የሚሰብኩትን አትስሚ፤ የጋብቻንም ግዴታ [ወይም ዋና ዓላማ] አስቢ፡፡ እነዚህን ግዴታዎች [ወይም ዓላማዎች] ስታውቂ የቤተሰብሽን ተግባራት ለማከናወን እንደ ምን ያለ ትዕግሥትና ጽናት እንደሚያስፈልግሽ ታውቂያለሽና፡፡ እንደ ሚስት እጅግ ጥንካሬን ገንዘብ የምታደርጊውም በዚህ መንገድ ነው፡፡

“ወንዶች እንዴት በቀላሉ የሚቈጡ መኾናቸውን በርግጥ ልታውቂ ይገባሻል፡፡ አይችሉም፤ ብዙ ጊዜም እንደ በረኻ አንበሳ ይኾናሉ፡፡ እንግዲህ ሚስት ጸንታ ልትቆምና የነፍስ ልዕልናዋን ልታሳይ የሚገባት በዚህች ቅጽበት ነው፡፡ አንበሳን የማስለመድ ሥራ መሥራት አለብሽ፡፡ አንበሳን የሚያስለምድ ሰው አንበሳ ሲያገሳ የሚያደርገው ምንድን ነው? ከየትኛውም ጊዜ በላይ ዝም ጸጥ ይላል፡፡ በጸጥታውና በርጋታውም የአንበሳውን ቊጣ ይቈጣጠራል፡፡ በርጋታና በለሆሳስ ኾኖ ያናግረዋል፤ ይደባብሰዋል፤ በቀስታ ያሻሸዋል፤ በጥቂት በጥቂቱም አንበሳው ቊጣውን ይተዋል፡፡

“ባልሽ ስሕተት ሲሠራ በፍጹም ልትነቅፊው፣ ልትንቂው ወይም ልታስነውሪው አይገባም፡፡ በተመሳሳይ መንገድ አንድ መሥራት ያለበትን ነገር ባይሠራና ከዚሁ የተነሣም ውጤቱ ደስ የማያሰኝ ቢኾን፣ ወይም እጅግ የምትፈልጊውና አግባብ ነው ብለሽ የምታስቢውን ባያደርግ እንኳን ባልሽን መናቅ ከአንቺ ልታርቂ ይገባል፡፡ ክፉዎች አጋንንት ዘወትር ቤታችሁን ለማፍረስና የጥንዶች መንፈሳዊ አንድነትን ለመበተን እንደሚሞክሩ ዕወቂ፡፡”

( ከገብረ_እግዚአብሔር_ኪደ ከትንሿ ቤተክርስቲያን መጽሐፍ የተገኘ)
See more posts
Telegram Channel