
Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች
The interest of this Channel is giving continuous information about housing projects (40/60&20/80) & other Real Estates Updates. This page is not a gov’t page.
Recent Posts
የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ
ከዛሬ መጋቢት 14/2017 ዓ/ም ምሽት 12 ሠዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ ተደርጓል።
በዚህም መሰረት ፦
➡ አንድ ሊትር ቤንዚን
112 ብር ከ67 ሳንቲም
➡ አንድ ሊትር ነጭ ናፍጣ
107 ብር ከ93 ሳንቲም
➡ አንድ ሊትር ኬሮሲን
107 ብር ከ93 ሳንቲም
➡ የአውሮፕላን ነዳጅ
113 ብር ከ20 ሳንቲም
➡ አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ
106 ብር ከ75 ሳንቲም
➡ አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ
109 ብር ከ22 ሳንቲም ገብቷል።
ከዛሬ መጋቢት 14/2017 ዓ/ም ምሽት 12 ሠዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ ተደርጓል።
በዚህም መሰረት ፦
➡ አንድ ሊትር ቤንዚን
112 ብር ከ67 ሳንቲም
➡ አንድ ሊትር ነጭ ናፍጣ
107 ብር ከ93 ሳንቲም
➡ አንድ ሊትር ኬሮሲን
107 ብር ከ93 ሳንቲም
➡ የአውሮፕላን ነዳጅ
113 ብር ከ20 ሳንቲም
➡ አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ
106 ብር ከ75 ሳንቲም
➡ አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ
109 ብር ከ22 ሳንቲም ገብቷል።
ፖሊስ ጣብያዎች ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ገንዘብ በመቅጣት ገቢ እንዲያስገቡ መታዘዛቸው ተሰማ
- "እያንዳንዱ የፖሊስ ጣብያ በቅጣት የሚያስገባው የገንዘብ ኮቴ ተጥሎበታል፣ በዛሬው እለት ብቻ 4.2 ሚልየን ብር ተሰብስቧል"
(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የፖሊስ አባላት ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ድርጅቶችን እና ግለሰቦችን ገንዘብ በመቅጣት ገቢ እንዲያስገቡ መታዘዛቸው ታውቋል።
ለመሠረት ሚድያ የደረሰው ጥቆማ እንደሚያሳየው የየክፍለ ከተማው ስራ አስፈፃሚዎች በየጊዜው የፖሊስ አዛዦችን እየሰበሰቡ ገንዘብ በተለይ ከነጋዴዎች እና ድርጅቶች በአስገዳጅ ሁኔታ እንዲሰበስቡ ትዕዛዝ ተላልፎላቸዋል።
"በእያንዳንዱ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ከላይ የተወሰነ ኮታ አለ፣ ያንን በተሰጠን ጊዜ ገደብ ሰብስበን ማስገባት ግዴታችን ነው" ብለው ቃላቸውን የሰጡ አንድ የፖሊስ ኢንስፔክተር በዚህ ምክንያት ፖሊስ መደበኛ ስራውን ጥሎ ቤት ለቤት እና በየድርጅቱ ገንዘብ ሲጠይቅ ይውላል ብለዋል።
ሌላኛው ደግሞ "ገንዘብ ከምንሰበስብባቸው መንገዶች መሃከል ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ገንዘብ መቅጣት፣ አስገዳጅ የህዳሴ ኩፖን ማስገዛት፣ ለኮሪደር ልማት በሚል ከነጋዴዎች መዋጮ መጠየቅ ናቸው ያልተስማማ ካለ የንግድ ፈቃድ እስከመታገድ ይደርሳል" በማለት ሁኔታውን አስረድተዋል።
ከሰሞኑ በርካታ የመንግስት ሚድያዎች ፍሳሽ የለቀቁ፣ መንገድ ያበላሹ፣ እና ያልተፈቀደ ስራ የሰሩ በማለት ድርጅቶች ከአስር ሺዎች እስከ መቶ ሺህ ብሮች እንደተቀጡ መዘገባቸው ይታወሳል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዛሬ ባወጣው አንድ መግለጫ በዛሬው ቀን ብቻ ድርጅቶችን እና ግለሰቦችን 4.2 ሚልዮን ብር እንደቀጣ አስታውቋል።
ባለስልጣኑ እንዳለው በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ 1.3 ሚልዮን ብር፣ በአቃቂ ክ/ከተማ 800 ሺህ ብር፣ በየካ ክፍለ ከተማ 600 ሺህ ብር፣ በቦሌ ክፍለ ከተማ 600 ሺህ ብር፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ 500 ሺህ ብር በዛሬው እለት ብቻ ከቅጣት ተሰብስቧል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
- "እያንዳንዱ የፖሊስ ጣብያ በቅጣት የሚያስገባው የገንዘብ ኮቴ ተጥሎበታል፣ በዛሬው እለት ብቻ 4.2 ሚልየን ብር ተሰብስቧል"
(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የፖሊስ አባላት ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ድርጅቶችን እና ግለሰቦችን ገንዘብ በመቅጣት ገቢ እንዲያስገቡ መታዘዛቸው ታውቋል።
ለመሠረት ሚድያ የደረሰው ጥቆማ እንደሚያሳየው የየክፍለ ከተማው ስራ አስፈፃሚዎች በየጊዜው የፖሊስ አዛዦችን እየሰበሰቡ ገንዘብ በተለይ ከነጋዴዎች እና ድርጅቶች በአስገዳጅ ሁኔታ እንዲሰበስቡ ትዕዛዝ ተላልፎላቸዋል።
"በእያንዳንዱ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ከላይ የተወሰነ ኮታ አለ፣ ያንን በተሰጠን ጊዜ ገደብ ሰብስበን ማስገባት ግዴታችን ነው" ብለው ቃላቸውን የሰጡ አንድ የፖሊስ ኢንስፔክተር በዚህ ምክንያት ፖሊስ መደበኛ ስራውን ጥሎ ቤት ለቤት እና በየድርጅቱ ገንዘብ ሲጠይቅ ይውላል ብለዋል።
ሌላኛው ደግሞ "ገንዘብ ከምንሰበስብባቸው መንገዶች መሃከል ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ገንዘብ መቅጣት፣ አስገዳጅ የህዳሴ ኩፖን ማስገዛት፣ ለኮሪደር ልማት በሚል ከነጋዴዎች መዋጮ መጠየቅ ናቸው ያልተስማማ ካለ የንግድ ፈቃድ እስከመታገድ ይደርሳል" በማለት ሁኔታውን አስረድተዋል።
ከሰሞኑ በርካታ የመንግስት ሚድያዎች ፍሳሽ የለቀቁ፣ መንገድ ያበላሹ፣ እና ያልተፈቀደ ስራ የሰሩ በማለት ድርጅቶች ከአስር ሺዎች እስከ መቶ ሺህ ብሮች እንደተቀጡ መዘገባቸው ይታወሳል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዛሬ ባወጣው አንድ መግለጫ በዛሬው ቀን ብቻ ድርጅቶችን እና ግለሰቦችን 4.2 ሚልዮን ብር እንደቀጣ አስታውቋል።
ባለስልጣኑ እንዳለው በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ 1.3 ሚልዮን ብር፣ በአቃቂ ክ/ከተማ 800 ሺህ ብር፣ በየካ ክፍለ ከተማ 600 ሺህ ብር፣ በቦሌ ክፍለ ከተማ 600 ሺህ ብር፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ 500 ሺህ ብር በዛሬው እለት ብቻ ከቅጣት ተሰብስቧል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
የኤሌትሪክ መኪና ቻርጅ ለማድረግ ሰልፍ
የት ነው?
ህዝብ ተራብኩ፣ ተቸገርኩ፣ መኖር ከበደኝ፣ ልጆቼን ማስተማር አቃተኝ ሲል ይህን የእዳ መአት በየግዜው መጫን ማለት ህብረተሰቡ ከዳቦ ውጭ እንዳያስብ አርጎ ለመግዛት ካልሆነ ምን ይባላል?
በየሰፈሩ ለኮሪደር ልማት፣ ለብልፅግና ፅ/ቤት ማሰርያ፣ ለቀይ መስቀል፣ ለሚሊሺያ፣ ለመንገድ ግንባታ... ወዘተ እየተባለ ፍዳውን የሚያየው ሳያንስ አሁን ደግሞ አደጋ ለመከላከል።
@EliasMeseret
በየሰፈሩ ለኮሪደር ልማት፣ ለብልፅግና ፅ/ቤት ማሰርያ፣ ለቀይ መስቀል፣ ለሚሊሺያ፣ ለመንገድ ግንባታ... ወዘተ እየተባለ ፍዳውን የሚያየው ሳያንስ አሁን ደግሞ አደጋ ለመከላከል።
@EliasMeseret
#ቅጣቱ ወደ 60 ሚሊየን ብር ከፍ አለ!
የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት፤ በሕንጻ ግንባታ ወቅት የአደጋ ጊዜ መውጫ አሳንሰር እና ሌሎች የግንባታ መስፈርቶችን በማያሟሉ ገንቢዎች ላይ የሚጣለው ከ3 እስከ 5 ሚሊየን ብር ቅጣት አሁን ላይ ወደ 60 ሚሊየን ብር ከፍ መደረጉ ተገልጿል፡፡
የአዲስ አበባ ግንባታ ፈቃድ እና ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ደሲሳ ለአሐዱ እንደገለጹት፤ ይህ የገንዘብ ቅጣት እንዲሻሻል የተደረገው መመሪያዎችን የማያሟሉ አካላትን ቁጥር ለመቀነስ እንዲሁም ሕንጻዎች በዲዛይንም ሆነ በግንባታ ደረጃቸውን ጠብቀው እንዲሰሩ ለማድረግ ነው።
"በከተማዋ በ2016 በተደረገ ዳሰሳ ከ52 ሺሕ 600 በላይ ሕንጻዎች ይገኛሉ" ያሉት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ በእነዚህ ሕንጻዎች ላይ በየአራት ዓመቱ የሚደረገው ፍተሻ አሁን ወደ ሁለት ዓመት ዝቅ እንዲል መደረጉን ጨምረው ተናግረዋል፡፡
አሐዱም "በዚህ አዲስ አሠራር መሠረት ምን ያክል ገንቢዎች ተጠያቂ ተደረጉ?" ሲል ላነሳው ጥያቄ ቁጥራዊ መረጃዎችን ከመስጠት የተቆጠቡት አቶ ገዛኸኝ፤ ነገር ግን "ከሕንጻዎች የአደጋ ጊዜ መውጫ ብረቶች መስፈርት (ስታንዳርድ) ጋር በተያያዘ የሚወስነው የሕንጻው ከፍታና የሚይዘው ክብደት ነው" ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ይህ መስፈርት የሚሰራው ለአገልግሎት ሰጭ ተቋማት ከ12 ሜትር እና ለመኖሪያ ቤቶች ከ20 ሜትር በላይ የሆኑ ሕንጻዎች ላይ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
አሐዱሬዲዮ
የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት፤ በሕንጻ ግንባታ ወቅት የአደጋ ጊዜ መውጫ አሳንሰር እና ሌሎች የግንባታ መስፈርቶችን በማያሟሉ ገንቢዎች ላይ የሚጣለው ከ3 እስከ 5 ሚሊየን ብር ቅጣት አሁን ላይ ወደ 60 ሚሊየን ብር ከፍ መደረጉ ተገልጿል፡፡
የአዲስ አበባ ግንባታ ፈቃድ እና ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ደሲሳ ለአሐዱ እንደገለጹት፤ ይህ የገንዘብ ቅጣት እንዲሻሻል የተደረገው መመሪያዎችን የማያሟሉ አካላትን ቁጥር ለመቀነስ እንዲሁም ሕንጻዎች በዲዛይንም ሆነ በግንባታ ደረጃቸውን ጠብቀው እንዲሰሩ ለማድረግ ነው።
"በከተማዋ በ2016 በተደረገ ዳሰሳ ከ52 ሺሕ 600 በላይ ሕንጻዎች ይገኛሉ" ያሉት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ በእነዚህ ሕንጻዎች ላይ በየአራት ዓመቱ የሚደረገው ፍተሻ አሁን ወደ ሁለት ዓመት ዝቅ እንዲል መደረጉን ጨምረው ተናግረዋል፡፡
አሐዱም "በዚህ አዲስ አሠራር መሠረት ምን ያክል ገንቢዎች ተጠያቂ ተደረጉ?" ሲል ላነሳው ጥያቄ ቁጥራዊ መረጃዎችን ከመስጠት የተቆጠቡት አቶ ገዛኸኝ፤ ነገር ግን "ከሕንጻዎች የአደጋ ጊዜ መውጫ ብረቶች መስፈርት (ስታንዳርድ) ጋር በተያያዘ የሚወስነው የሕንጻው ከፍታና የሚይዘው ክብደት ነው" ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ይህ መስፈርት የሚሰራው ለአገልግሎት ሰጭ ተቋማት ከ12 ሜትር እና ለመኖሪያ ቤቶች ከ20 ሜትር በላይ የሆኑ ሕንጻዎች ላይ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
አሐዱሬዲዮ
"ይሄ ማ በቅቅል ብቻ አይታለፍም"😂
በአዲስ አበባ ከተማ 18 ሄክታር መሬት ለሊዝ ጨረታ ሊቀርብ ነው
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ፤ በጥቅሉ 18 ሄክታር ስፋት ያላቸው 427 ቦታዎችን ለሊዝ ጨረታ ሊያቀርብ ነው። በመዲናይቱ ዘጠኝ ክፍለ ከተሞች የሚገኙት እነዚህ ቦታዎች፤ ለመኖሪያ እና ለንግድ አገልግሎት የሚውሉ መሆናቸው ተገልጿል።
በከተማይቱ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የመሬት ዝግጅት እና ባንክ ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ተስፋዬ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት፤ ለጨረታ የሚቀርቡት ቦታዎች “በተለያየ አግባብ ወደ መሬት ባንክ የገቡ ይዞታዎች” ናቸው። በአሁኑ ዙር ጨረታ በቦሌ እና ልደታ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የመሬት ይዞታዎች እንዳልተካተቱ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
ለጨረታ የሚቀርቡት ቦታዎች ዝርዝር፤ “አዲስ ልሳን” ጋዜጣ ማግኘት እንደሚቻል የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ይህንን ተከትሎ የጨረታ ሰነድ ሽያጩ “ከእጅ ንኪኪ በጸዳ መልኩ” ከመጪው ሰኞ መጋቢት 1 እስከ መጋቢት 12 ድረስ ባሉት ቀናቶች የሚከናወን መሆኑንም ጠቁሟል።
🔴ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️https://ethiopiainsider.com/2025/15278/
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ፤ በጥቅሉ 18 ሄክታር ስፋት ያላቸው 427 ቦታዎችን ለሊዝ ጨረታ ሊያቀርብ ነው። በመዲናይቱ ዘጠኝ ክፍለ ከተሞች የሚገኙት እነዚህ ቦታዎች፤ ለመኖሪያ እና ለንግድ አገልግሎት የሚውሉ መሆናቸው ተገልጿል።
በከተማይቱ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የመሬት ዝግጅት እና ባንክ ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ተስፋዬ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት፤ ለጨረታ የሚቀርቡት ቦታዎች “በተለያየ አግባብ ወደ መሬት ባንክ የገቡ ይዞታዎች” ናቸው። በአሁኑ ዙር ጨረታ በቦሌ እና ልደታ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የመሬት ይዞታዎች እንዳልተካተቱ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
ለጨረታ የሚቀርቡት ቦታዎች ዝርዝር፤ “አዲስ ልሳን” ጋዜጣ ማግኘት እንደሚቻል የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ይህንን ተከትሎ የጨረታ ሰነድ ሽያጩ “ከእጅ ንኪኪ በጸዳ መልኩ” ከመጪው ሰኞ መጋቢት 1 እስከ መጋቢት 12 ድረስ ባሉት ቀናቶች የሚከናወን መሆኑንም ጠቁሟል።
🔴ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️https://ethiopiainsider.com/2025/15278/
ለአዲስ አበባ ባለጓሮዎች
በ2016 ዓ.ም በተሻሻለው የአዲስ አበባ የህንፃ መመሪያ መሰረት በከተማ አስተዳደሩ ክልል ውስጥ የሚገኙ አርሶ አደሮች በይዞታቸው ላይ ማልማት የሚችሉበትን ህጋዊ አሰራር ያሳያል፡፡
በመመሪያው ከገጽ 34 እስከ 36 በተገለፀው መሰረት ከ1,000 ካሬ በታች ላሉ ይዞታቸው ስፋት 80 በመቶ ያልበለጠ፣
ከ1,001 እስከ 2,000 ካሬ ሜትር ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 70 በመቶ ያልበለጠ፣
ከ2,001 እስከ 3,000 ካሬ ሜትር ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 50 በመቶ ያልበለጠ፣
ከ3,001 እስከ 4,000 ካሬ ሜትር ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 25 በመቶ ያልበለጠ፣
ከ4,001 እስከ 5,000 ካሬ ሜትር ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 20 በመቶ ያልበለጠ እንዲሁም
ከ5,001 ካሬ ሜትር በላይ ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 20 በመቶ ያልበለጠ
ነገር ግን አጠቃላይ ግንባታው ከ2,000 ካሬ ሜትር በላይ መብለጥ የለበትም ሲል ይደነግጋል፡፡
ይህ ማለት ቀደም ብሎ አርሶ አደሩ ማልማት የሚችለው 5% በሚል ተቀምጦ የነበረው አሰራር ከላይ በተዘረዘሩት አገላለፆች ተቀይሯል ማለት ነው፡፡
የአርሶ አደር ማቋቋምና ሬጉላቶሪ ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ወ/ሮ ሎኮ ዳለቻ አርሶ አደሩ ለረጂም ጊዜ ሲጠይቅ የነበረው ጥያቄ መልስ ያገኘ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ነገር ግን ሌብነትና ብልሹ አሰራርን መከላከል ይገባል ብለዋል፡፡
አያይዘውም በየደረጃው ያሉ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች መመሪያው ሳይሸራረፍ መተግበር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የአርሶ አደር ማቋቋምና ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ረጋሣ ባይሳ በበኩላቸው መመሪያውን ለክፍለ ከተሞች እንዳወረዱ፤ በባለሙያም አተገባበሩ ላይ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ ገልፀዋል፡፡
በአዲስ አበባ አርሶአደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን
በ2016 ዓ.ም በተሻሻለው የአዲስ አበባ የህንፃ መመሪያ መሰረት በከተማ አስተዳደሩ ክልል ውስጥ የሚገኙ አርሶ አደሮች በይዞታቸው ላይ ማልማት የሚችሉበትን ህጋዊ አሰራር ያሳያል፡፡
በመመሪያው ከገጽ 34 እስከ 36 በተገለፀው መሰረት ከ1,000 ካሬ በታች ላሉ ይዞታቸው ስፋት 80 በመቶ ያልበለጠ፣
ከ1,001 እስከ 2,000 ካሬ ሜትር ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 70 በመቶ ያልበለጠ፣
ከ2,001 እስከ 3,000 ካሬ ሜትር ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 50 በመቶ ያልበለጠ፣
ከ3,001 እስከ 4,000 ካሬ ሜትር ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 25 በመቶ ያልበለጠ፣
ከ4,001 እስከ 5,000 ካሬ ሜትር ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 20 በመቶ ያልበለጠ እንዲሁም
ከ5,001 ካሬ ሜትር በላይ ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 20 በመቶ ያልበለጠ
ነገር ግን አጠቃላይ ግንባታው ከ2,000 ካሬ ሜትር በላይ መብለጥ የለበትም ሲል ይደነግጋል፡፡
ይህ ማለት ቀደም ብሎ አርሶ አደሩ ማልማት የሚችለው 5% በሚል ተቀምጦ የነበረው አሰራር ከላይ በተዘረዘሩት አገላለፆች ተቀይሯል ማለት ነው፡፡
የአርሶ አደር ማቋቋምና ሬጉላቶሪ ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ወ/ሮ ሎኮ ዳለቻ አርሶ አደሩ ለረጂም ጊዜ ሲጠይቅ የነበረው ጥያቄ መልስ ያገኘ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ነገር ግን ሌብነትና ብልሹ አሰራርን መከላከል ይገባል ብለዋል፡፡
አያይዘውም በየደረጃው ያሉ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች መመሪያው ሳይሸራረፍ መተግበር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የአርሶ አደር ማቋቋምና ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ረጋሣ ባይሳ በበኩላቸው መመሪያውን ለክፍለ ከተሞች እንዳወረዱ፤ በባለሙያም አተገባበሩ ላይ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ ገልፀዋል፡፡
በአዲስ አበባ አርሶአደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን
አያት መንግሥት ባለበት አገር የገዙትን ሱቅ አላስረክብም ብሎ ለ18 ዓመታት እያሰቃያቸው መሆኑን ገዥዎች ተናገሩ
የሚመለከተው የመንግሥት አካል መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል
‹‹ያሉትን ችግሮች በንግግር እንፍታ ብለናቸዋል››
አያት ሪል ስቴት
ከአያት አክሲዮን ማኅበር ከ18 ዓመታት በፊት የንግድ ሱቆችን ግዥ ሲፈጽሙ በገባው ውል መሠረት ሙሉ ለሙሉ ገንብቶ በ18 ወራት ሊያስረክባቸው ስምምነት የፈጸሙ ቢሆንም፣ የተለያዩ ምክንያቶችን በመስጠትና ምላሽ በመንፈግ ላለፉት 18 ዓመታት እያሰቃያቸው መሆኑንና ሊያስረክባቸው እንዳልቻለ ገልጸው፣ መንግሥት ባለበት አገር መበደል ስለሌለባቸው የሚመለከተው አካል መፍትሔ እንዲሰጣቸው ገዥዎች ጠየቁ፡፡
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ አሥር አያት ባቡር ጣቢያ አካባቢ ከ550 በላይ የንግድ ሱቆች...
ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/138841/
የሚመለከተው የመንግሥት አካል መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል
‹‹ያሉትን ችግሮች በንግግር እንፍታ ብለናቸዋል››
አያት ሪል ስቴት
ከአያት አክሲዮን ማኅበር ከ18 ዓመታት በፊት የንግድ ሱቆችን ግዥ ሲፈጽሙ በገባው ውል መሠረት ሙሉ ለሙሉ ገንብቶ በ18 ወራት ሊያስረክባቸው ስምምነት የፈጸሙ ቢሆንም፣ የተለያዩ ምክንያቶችን በመስጠትና ምላሽ በመንፈግ ላለፉት 18 ዓመታት እያሰቃያቸው መሆኑንና ሊያስረክባቸው እንዳልቻለ ገልጸው፣ መንግሥት ባለበት አገር መበደል ስለሌለባቸው የሚመለከተው አካል መፍትሔ እንዲሰጣቸው ገዥዎች ጠየቁ፡፡
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ አሥር አያት ባቡር ጣቢያ አካባቢ ከ550 በላይ የንግድ ሱቆች...
ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/138841/
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ከአያት ሪል ስቴት ሱቅ የገዙ ሰዎች በድርጅቱ ላይ አቤቱታ አሰሙ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አያት ሾፒንግ ሞል በሚል በተገነባው ህንፃ ውስጥ ሱቅ የገዙት የዛሬ 16 አመት እንደነበር አቤቱታ አቅራቢዎቹ ገልፀዋል፡፡ በወቅቱ ድርጅቱ በሁለት አመት ውስጥ ግንባታውን አጠናቆ እንደሚያስረክባቸው ቃል እንደገባላቸውም አስረድተዋል፡፡
የአያት ሞል ሱቅ ባለቤቶች ማህበር ፀሀፊ ሩት ግርማይ ስትናገር ‹‹እኛ የማህበሩ አባላት በህጋዊ መንገድ ሱቅ የገዛንና ውል የፈፀምን ነን፡፡ ነገር ግን ድርጅቱ ተገቢውን መሰረተ ልማት አሟልቶ ባለማጠናቀቁ ሱቃችንን ለመረከብ ፈቃደኛ ባለመሆናችን ተዘግቶ ይገኛል›› ብላለች፡፡ እንደገለፀችውም በህንፃው ውስጥ ካልተጠናቀቁት መሰረተ ልማቶች መካከል መብራት፣ ውሀ፣ መፀዳጃ ቤት፣ መኪና ማቆሚያና ሊፍት ይገኙበታል፡፡ የህንፃው ግንባታ ረጅም ጊዜ በመቆየቱ አንዳንድ የማህበሩ አባላት በራሳቸው ወጪ አጠናቀው ስራ መጀመራቸውን ሩት ገልፃለች፡፡
ጉዳዩን ወደፍርድ ቤት ለመውሰድ ቢፈልጉም የገንዘብ እጥረት እንዳለባቸው ጠቅሳም በአሁኑ ወቅት ለሚመለከታቸው የመንግስት መስሪያ ቤቶች አቤቱታ በማቅረብ ላይ ቢሆኑም ምንም መፍትሄ አለማግኘታቸውን አስርታለች፡፡ የአያት ሪል ስቴት ቦርድ ምክትል ሊቀመንበር አቶ አብይ ማሞ ስለጉዳዩ ከዘሪፖርተር ተጠይቀው ሲመልሱ ‹‹እኛ ሱቅ ገዢዎቹን በመነጋገርና በውይይት ችግሩን እንድንፈታ ጠይቀናቸው ነበር፡፡ እነሱ ግን ጉዳዩን ወደተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች መውሰድን መርጠዋል›› ካሉ በኋላ ጉዳዩን ለመፍታት በሂደት ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡
የአያት ሞል ሱቅ ባለቤቶች ማህበር ፀሀፊ ሩት ግርማይ ስትናገር ‹‹እኛ የማህበሩ አባላት በህጋዊ መንገድ ሱቅ የገዛንና ውል የፈፀምን ነን፡፡ ነገር ግን ድርጅቱ ተገቢውን መሰረተ ልማት አሟልቶ ባለማጠናቀቁ ሱቃችንን ለመረከብ ፈቃደኛ ባለመሆናችን ተዘግቶ ይገኛል›› ብላለች፡፡ እንደገለፀችውም በህንፃው ውስጥ ካልተጠናቀቁት መሰረተ ልማቶች መካከል መብራት፣ ውሀ፣ መፀዳጃ ቤት፣ መኪና ማቆሚያና ሊፍት ይገኙበታል፡፡ የህንፃው ግንባታ ረጅም ጊዜ በመቆየቱ አንዳንድ የማህበሩ አባላት በራሳቸው ወጪ አጠናቀው ስራ መጀመራቸውን ሩት ገልፃለች፡፡
ጉዳዩን ወደፍርድ ቤት ለመውሰድ ቢፈልጉም የገንዘብ እጥረት እንዳለባቸው ጠቅሳም በአሁኑ ወቅት ለሚመለከታቸው የመንግስት መስሪያ ቤቶች አቤቱታ በማቅረብ ላይ ቢሆኑም ምንም መፍትሄ አለማግኘታቸውን አስርታለች፡፡ የአያት ሪል ስቴት ቦርድ ምክትል ሊቀመንበር አቶ አብይ ማሞ ስለጉዳዩ ከዘሪፖርተር ተጠይቀው ሲመልሱ ‹‹እኛ ሱቅ ገዢዎቹን በመነጋገርና በውይይት ችግሩን እንድንፈታ ጠይቀናቸው ነበር፡፡ እነሱ ግን ጉዳዩን ወደተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች መውሰድን መርጠዋል›› ካሉ በኋላ ጉዳዩን ለመፍታት በሂደት ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡
ማስታወቂያ በአዲስ አበባ ከተማ ለምትገኙ የሪል እስቴት አልሚዎች በሙሉ
በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሪል እስቴት ልማት ስራ ላይ የተሰማራችሁ አልሚዎች በሪል አስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ እንዲሁም ይህንን ለማስፈጸም በወጣው ረቂቅ ደንብ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ስለሚካሄድ የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ባምቢስ አጠገብ በሚገኘው በዲል ኦፖል ሆቴል ከጠዋቱ 2፡00 ሰአት ጀምሮ ባለቤቶች ወይም ህጋዊ ወኪል የሆናችሁ ሁሉ በመገኘት የውይይቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ ጥሪ እናሰተላልፋለን፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ
በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሪል እስቴት ልማት ስራ ላይ የተሰማራችሁ አልሚዎች በሪል አስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ እንዲሁም ይህንን ለማስፈጸም በወጣው ረቂቅ ደንብ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ስለሚካሄድ የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ባምቢስ አጠገብ በሚገኘው በዲል ኦፖል ሆቴል ከጠዋቱ 2፡00 ሰአት ጀምሮ ባለቤቶች ወይም ህጋዊ ወኪል የሆናችሁ ሁሉ በመገኘት የውይይቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ ጥሪ እናሰተላልፋለን፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ
ችሏል
#CapitalNews የመንግስት ቤቶች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ስራ ባለመጠናቀቁ ቤቶቹ በህገወጥ መልኩ ወደ ግለሰቦች እየዞሩ ይገኛል ተባለ
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ
የመንግስት ቤቶች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ስራ አለመጠናቀቁ ቤቶችን በህገወጥ መልኩ ወደግለሰቦች እንዲዞሩ በር እየከፈተ እንደሚገኝ አስታውቋል።
የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባ ሙሉ በሙሉ
ባለመጠናቀቁና አዳዲስ ውል ምዝገባዎች መረጃ እየተለዩና እየተደራጁ ባለመሆኑ ስራዎችን በተቋሙ የመረጃ ቋት ላይ ለመጫን ክፍተት እየፈጠረ እንደሚገኝ ቢሮዉ ገልጿል።
ለካፒታል የደረሰዉ መረጃ እንደሚያመላክተዉ አሁን ላይ ከ150 ሺህ በላይ የመንግስት መኖርያና የንግድ ቤቶች መረጃ በለማው ቴክኖሎጂ ወደ መረጃ ቋት ማስገባት እንደተቻለ እና ከነዚህ ውስጥ 93 ሺህ 350 የሚሆኑ ቤቶች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንደተሰራላቸው ተጠቁሟል።
የተቋሙ የ 6 ወር ሪፖርት እንደሚያሳየዉ እስከአሁን ባለው ጊዜ ከ 495 ሺህ 745 በላይ ቤቶችን የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባ ተከናዉኗል።
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ
የመንግስት ቤቶች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ስራ አለመጠናቀቁ ቤቶችን በህገወጥ መልኩ ወደግለሰቦች እንዲዞሩ በር እየከፈተ እንደሚገኝ አስታውቋል።
የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባ ሙሉ በሙሉ
ባለመጠናቀቁና አዳዲስ ውል ምዝገባዎች መረጃ እየተለዩና እየተደራጁ ባለመሆኑ ስራዎችን በተቋሙ የመረጃ ቋት ላይ ለመጫን ክፍተት እየፈጠረ እንደሚገኝ ቢሮዉ ገልጿል።
ለካፒታል የደረሰዉ መረጃ እንደሚያመላክተዉ አሁን ላይ ከ150 ሺህ በላይ የመንግስት መኖርያና የንግድ ቤቶች መረጃ በለማው ቴክኖሎጂ ወደ መረጃ ቋት ማስገባት እንደተቻለ እና ከነዚህ ውስጥ 93 ሺህ 350 የሚሆኑ ቤቶች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንደተሰራላቸው ተጠቁሟል።
የተቋሙ የ 6 ወር ሪፖርት እንደሚያሳየዉ እስከአሁን ባለው ጊዜ ከ 495 ሺህ 745 በላይ ቤቶችን የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባ ተከናዉኗል።
#CapitalNews የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጣራና የግድግዳ ግብርን የመሰብሰብ ስልጣን ያለው መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጣራና የግድግዳ ግብርን የመሰብሰብ በአዋጅ የተሰጠው ስልጣን ያለው ሲሆን፣ ይህን ግብር ከመሰብሰብ የሚከለክል ምንም አይነት ህጋዊ አካል እንደሌለ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል።
ይህንን የተናገሩት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ2017 ዓ.ም 4ኛ የስራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን እየተካሄደ ባለበት ወቅት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ ነው።
ከንቲባዋ የጣራና የግድግዳ ግብርን በተመለከተ የምክር ቤት አባላት ላነሷቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ፣ የጣራና የግድግዳ ግብር አዋጅ በ1968 ዓ.ም የወጣ አዋጅ መሆኑን አስታውሰዋል።
በወቅቱ የነበረው አሰራር አሁንም እንደቀጠለ ነው ያሉት ከንቲባዋ፣ ነገር ግን የተለወጠው ወቅቱን ያገናዘበ የዋጋ ተመን ብቻ ነው ብለዋል።
በተጨማሪም አዋጁ ሲወጣ የነበረው የኪራይ ዋጋ እና አሁን ያለው የኪራይ ዋጋ እኩል ባለመሆኑ አሁን የጨመረው ኪራዩ መሆኑን ጠቁመዋል።
የከተማ አስተዳደሩ የሚያስከፍለው ግብር ግን በትክክለኛ ዋጋው ሳይሆን ለመኖሪያ ቤት የዋጋውን ግማሽ እንዲሁም ለንግድ ቤቶች 75 በመቶ ብቻ እንደሆነ ከንቲባዋ አብራርተዋል።
በከተማዋ በግብር ስርዓት ውስጥ ያልነበሩ በርካታ ነዋሪዎች እንደነበሩ ያስታወሱት ከንቲባ አዳነች፣ በከተማዋ ካሉ 800 ሺህ ህንጻዎችና ቤቶች ግብር ይከፍሉ የነበሩት 120 ሺህ ብቻ እንደነበሩ ገልጸዋል።
በኢያሱ ዘካሪያስ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጣራና የግድግዳ ግብርን የመሰብሰብ በአዋጅ የተሰጠው ስልጣን ያለው ሲሆን፣ ይህን ግብር ከመሰብሰብ የሚከለክል ምንም አይነት ህጋዊ አካል እንደሌለ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል።
ይህንን የተናገሩት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ2017 ዓ.ም 4ኛ የስራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን እየተካሄደ ባለበት ወቅት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ ነው።
ከንቲባዋ የጣራና የግድግዳ ግብርን በተመለከተ የምክር ቤት አባላት ላነሷቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ፣ የጣራና የግድግዳ ግብር አዋጅ በ1968 ዓ.ም የወጣ አዋጅ መሆኑን አስታውሰዋል።
በወቅቱ የነበረው አሰራር አሁንም እንደቀጠለ ነው ያሉት ከንቲባዋ፣ ነገር ግን የተለወጠው ወቅቱን ያገናዘበ የዋጋ ተመን ብቻ ነው ብለዋል።
በተጨማሪም አዋጁ ሲወጣ የነበረው የኪራይ ዋጋ እና አሁን ያለው የኪራይ ዋጋ እኩል ባለመሆኑ አሁን የጨመረው ኪራዩ መሆኑን ጠቁመዋል።
የከተማ አስተዳደሩ የሚያስከፍለው ግብር ግን በትክክለኛ ዋጋው ሳይሆን ለመኖሪያ ቤት የዋጋውን ግማሽ እንዲሁም ለንግድ ቤቶች 75 በመቶ ብቻ እንደሆነ ከንቲባዋ አብራርተዋል።
በከተማዋ በግብር ስርዓት ውስጥ ያልነበሩ በርካታ ነዋሪዎች እንደነበሩ ያስታወሱት ከንቲባ አዳነች፣ በከተማዋ ካሉ 800 ሺህ ህንጻዎችና ቤቶች ግብር ይከፍሉ የነበሩት 120 ሺህ ብቻ እንደነበሩ ገልጸዋል።
በኢያሱ ዘካሪያስ